ካህኑ እያሱ ቢቆሽሽም ልብሱ ቢጠፋው ውበቱ ቢደክም ጉልበቱ አምላኩ አልተወውም አልቆበት ምህረቱ የጠላትን ምኞት አደረገበት ከንቱ ሰይጣን ቢከሰውም እያብጠነጠነ ሳር እየበተሰ ስር እየነቀለ ከሳሽም እራሱ ምስክር እራሱ ጌታ በቀባው ላይ ሲያስረዝም ምላሱን የተሰየመውን ከችሎቱ መሃል ቀና ብሎ ቢያየው የእርሱ አምላክ ኖሯል እኔ አልፈርድበትም ይሂድ ወደ ቤቱ ከስልጣኑ አይውረድ ይቀጥል ክህነቱ ተቀብዬዋለሁ ከነ ማንነቱ የጠላትን ምኞት አድርጊያለሁ ከንቱ ያዳም ዘር አፈር ስጋ ሰው መሆኑን ሳልዘነጋ የጠራሁን በእኔ ጸጋ ዋጋው አለ ከእኔው ጋር ይልቅ እድፋሙን ልብስ አውልቁለት ቶሎ መሸማቀቁ ይቅር ይሂድ ቀና ብሎ የክት ልብስ ይልበስ ከእግር እስከራሱ ከእንግዲህ ነጻ ነው ተፈቷል እያሱ አዝ:- በክርስቶስ ኢየሱስ ስራ በማመኔ የለብኝ የለብኝ የለብኝ ኩነኔ (2x) ቃሉ እንደሚናገር ጥንት በኦጽ አገር እዮብ የተባለ አንድ ሰው ነበር ፍፁምና ቅን ነው ከክፋት የራቀ አምላኩን ሚፈራ አመጽ ያላወቀ በልጅና በሃብት መባረኩን አይቶ ያሳጣው ጀመረ ቀናተኛው ቀንቶ ክሱን አዘነበው በራሱ እየማለ ስለባረከው ነው የፈራህ እያለ እስቲ የዙሪያውን አጥሩን አፍርስበት እጅህን ዘርጋና ያለውን ንካበት ያኔ ይሰድብሃል አንደበቱን ከፍቶ ማነው የሚታገስ ሃብቱን ተቀምቶ እያለ ቢከሰው ሃሰትን ቀምሞ እዮብ ድል አደረገ በእምነቱ ቆሞ ወዶ ሰጠኝ እግዚአብሔር ለምሥጋናው ለእርሱ ክብር ደግሞም ወዶ ከወሰደው አይጠየቅ ስልጣኑ ነው መልካሙን እንዳየ ክፉን ብንቀበል ሥሙ ብሩክ ይሁን ምሥጋናው ከፍ ይበል ሁለት እጥፍ ክሶ እግዚአብሔር ፈረደ እዮብ በድል ወጣ ከሳሽ ተዋረደ አዝ:- በክርስቶስ ኢየሱስ ስራ በማመኔ የለብኝ የለብኝ የለብኝ ኩነኔ (2x) እኔን ደስ ሲለኝ ጠላቴ ከፍቶታል መባረኬን ሲያይ እሳት ሆኖበታል ምክሩ ፈረሰበት አልሆነ እንዳሰበው እኔም ድሌን ላውጅ ጨምሮ ያንገብግበው መልካሙን ስራውን በእኔ የጀመረው ይፈጽምልኛል ጌታዬ ታማኝ ነው ሰይጣን ዘዋሪ ነው ሁሉን ያዳርሳል መክሰስ ልማዱ ነው ማንንም ይከሳል የክርስቶስን ደም ዋጋ አሳንሶ ከወንጌሉ ተስፋ ግማሹን ቀንሶ በተንኮል ሽንገላው እይተታለልን ሶኮነን ሲከሰስ ስንቱ ከቤት ዋለ ዘወትር የሚሸከም ጉድለት ድካምህን በሰማያት አለ ታላቅ ሊቀ ካህን እኔም ሆንኩኝ አንተም አንቺ ለሰይጣን ክስ አትመቺ አለንና ዋስ ጠበቃ ለሁላችን የሚበቃ ከእምነት አናፈግፍግ እንታመን እንጂ አለን በሰማያት ጽድቅ አማላጅ ሙሉ ዋጋ ከፍሎ በጸጋው አድኖኛል ሁሉን አሳልፎ ጽዮን ያገባኛል አዝ:- በክርስቶስ ኢየሱስ ስራ በማመኔ የለብኝ የለብኝ የለብኝ ኩነኔ (2x)