ተሻገሩ ብሎ አዞ በውኃ ሚያስበላ ኧረ እስቲ ንገሩኝ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆን ወይስ ሌላ መፈጸም አቅቶት ከአፉ የወጣውን ቃል ይቅርታ ጠይቆ ወይ ረዳት ፈልጐ እርሱ መች ያውቃል ይሄ ግን የማውቀው ጀምሮ ፈጻሚ ጠላት የመጣ እንደው እራሱን አስቀዳሚ እነርሱን ተዉአቸው እኔን ያዙኝ የሚል ከአውሬም መንጋጋ በጐቹን የሚያስጥል አዝ፦ አሁንስ ተስፋዬ ማነው ድጋፍ ምሶሶዬ ማነው አለኝታ ጋሻዬ ማነው መከታ አንባዬ ማነው ማነው (3x) እግዚአብሔር ነው ለአብርሃም ተናግሮ ነግሮ ለይሳቅ አጸና ለይሳቅ ተናግሮ ለያቆብ ፈጸመ እርሱ አይዋሽምና ዮሴፍ በግብጽ ምድር ቢወርድ ቢገባም ተሽጦ የፈርዖን መንግሥት ገዢ አደረገው ስርአት ለውጦ እግዚአብሔር ደክሟል አረጀ ያለ ማነው እኔስ እስከሚገባኝ ዛሬም ኤልሻዳይ ነው የእኔ እምነት ቢፈተን ቢለዋወጥበት እግዚአብሔር ግን ታምኖ አለ እዚያው ባለበት አዝ፦ አሁንስ ተስፋዬ ማነው ድጋፍ ምሶሶዬ ማነው አለኝታ ጋሻዬ ማነው መከታ አንባዬ ማነው ማነው (3x) እግዚአብሔር ነው በልዑል መጠጊያ አንባ መሽጐ ሚኖር ሁሉንም በሚችል አምላክ ጥላ ያድራል ከቶ አይሸበርም ከአዳኞች ወጥመድ ከሚያስደነግጥም ነገር ከክፉ ከልሎ ይታደገው የለ ሕያው እግዚአብሔር የቀኑ ፍላጻ የሌሊቱ ግርማ አደጋና ጋኔል ተጓዥ በጨለማ ሺ በሺ ሲያረግፈው ሲያስረግጠኝ ኖርኩኝ እኔም ከእርሱ በታች መቀጥቀጥ ተማርኩኝ አዝ፦ አሁንስ ተስፋዬ ማነው (ጌታ ነው) ድጋፍ ምሶሶዬ ማነው (ጌታ) አለኝታ ጋሻዬ ማነው (ጌታ ነው) መከታ አንባዬ ማነው (ጌታ ጌታ ጌታ) ማነው (3x) እግዚአብሔር ነው ማነው (3x) እግዚአብሔር ነው