ባማረ ባጌጠ ቤት ውስጥ ተሰይሚያለሁ በተዋበ ህዝብ ተከብቢያለሁ ዙሪያዬን የማየው ሁሉ ለዓይን ይስባል እኔ ግን ታምሜ ውበቴ ጠፍቶኛል ከቤትህ ውስጥ እያለሁ እኔ ጐድያለሁ ለሚያየኝ ለስሞ እኔ እንዳለሁ አለሁ ቤትህን ሲሞላው ዕልልታና ሆታ እኔን የሚያውከኝ የነፍሴ ጭንቀቷ የአንተ ቤት እኔ ነኝ የእኔ ቤት ሌላ ነው ቤተ ሰሪው በዝቶ መላ የሚለኝ ማነው ቀርበህ ሳለህ ከደጅ ልትመጣ ወዳጄ እንዴት ይሆን የማይህ እሩቅ አገር ሄጄ ያዳራሹ ውበት እኔን ሸፍኖኛል ግዑዝ ከእኔ በልጦ አልፎ ይኮንነኛል በጌጥ የታጀበ ቤቱ ተሰርቶ አልቆ ልብ ሁሉ በእጁ ነው የእኔን ቦታ ወስዶ ይበል እርሱም ይመር ቦታም አይጥበበን ግን ለታደሰ ቤት ምነው አጉል አጉል ሆነ እኔ ካልተደስኩኝ ካልሆንኩኝ እንደ ቤቱ ትርጉም የለሽ ኑሮ ድካም ነው ለከንቱ ቃሉ ቀርቧል እያልን ፍጻሜ የዘመን ከንቱ ቤት ስንሰራ ዘለዓለሙን ትተን ተላልፈን እንናገር አቤቱ አደራ የተጣልን እንዳንሆን እንደነበር ሥምህን ስንተጠራ ሥምህን ስንተጠራ ሥምህን አደራ የነበርን ሥምህን ስንተጠራ