ከአንተ በፊት የቆሰሉ ብዙ አሉ ለወንጌሉ እንደ እኔና እንደ አንተ በነጻነት ዘመን ያልተፈጠሩ ከአንቺ በፊት የተሰዉ ብዙ አሉ ለወንጌሉ እንደ እኔና እንደ አንቺ በነጻነት ዘመን ያልተፈጠሩ ከእኛ በፊት ብዙ አሉ የተሰዉ ለወንጌሉ እንደ እኛ በነጻነት ዘመን ያልተፈጠሩ ሳይሉ ችግሬን ጨርቄን ማቄን በጽድቅ የኖሩ በጌታ የተጉ ለጌታ የኖሩ በሰው የተጠሉ አቤት የሮጡለትን ያዩታል ከወደላይ የክብሩ ጌታ ሲያከብራቸው በሠማይ አቤት ያዩታል ጌታን ፊት ለፊት ሳያዩት ያመኑትን የናፈቁትን በነፍሳቸው የጨከኑት በሥጋቸው ያከበሩት አይገኝም አክሊላቸው በሠማይ ነው ክፍያቸው አቤት የሮጡለትን ያዩታል ከወደላይ ሆነው የባርነት ባሪያ ወጥተው ከሰውነት ተራ የእኔ የሚሉት የሌላቸው ልሩጥ ለእኔም ማያቃቸው ለወንጌል የቆሙ ለወንጌል የቀኑ ገንዘብ የማይደፍራቸው ሰልፍ ብርታታቸው አቤት የሮጡለትን ያዩታል ከወደላይ የክብሩ ጌታ ሲያከብራቸው በሠማይ አቤት ያዩታል ጌታን ፊት ለፊት ሳያዩት ያመኑትን የናፈቁት በነፍሳቸው የጨከኑት በሥጋቸው ያከበሩት አይገኝም አክሊላቸው በሠማይ ነው ክፍያቸው አቤት ያዩታል ጌታን ፊት ለፊት ማነው ታዲያ የዘምኔ አርበኛ ለጌታ ነገር ያልተኛ ብድራቱንስ ያልተቀበለ እውነት ለወንጌል የጨከነ በነጻነት ዘመን ራሱን የሰዋ ለጥቅም ያልኖረ በእምነቱ የጸና ማነው የዘምኔ ወንጌል ነጋሪ በተግባር የታየ የጽድቅ ተባባሪ ያልሆነ በፍፁም የነጻነት ባሪያ ከቶ ያልተገኘ እዚህ ሲሉት እዚያ ማነው የአቋም ሰው ዘመን ተሻጋሪ ሰልፍ እየበረታ ወንጌሉን ዘማሪ ማነው የዘመኔ ባለ አክሊል ተረኛ ለራሱ ያልኖረ ከሥጋው ጠበኛ ሞትን ጥቅሜ ብሎ በነፍሱ የጨከነ ግራ ቀኝ ያላየ ለቃሉ የታመነ ማነው የዘምኔ አርበኛ ማነው አቤት የሮጡለትም ያዩታል ከወደላይ የክብሩ ጌታ ሲያከብራቸው በሠማይ