በሰው ክፋት ማዕበል ምድር ስትናወጥ ፈጣሪ እንኳን በሰራው ፍጡር እስኪጸጸት የአንድ ኖህ ጎዳና አካሄድ ቢቀና የሰው ህይወት አልቀጠለም ወይ እንደገና በውሸት ከተማ እውነት እንግዳ ነው መስሎ ጸጉረ ልውጥ የሚያውቀው ሞኝ ነው እውነትን በተቀማ ትውልድ ማን ይሆን የእውነት ዘመድ ሁሉ ገሸሽ ሲል የአመጽ ቤት ሲደራ ማን አብሮ ይዘልቃል ከባይተዋር ጋራ እንደውሃና ዘይት አይደሉም ወይ እውነትና ሃሰት ምን አንዱ ቢበዛ መቼም አያብሩም ዘላለም በርቀት በጊዜም ፈተና ወደቅክ ሚለው የለም በእሳት ንዳድ አልፎ አመድ አያውቀውም በልዩነት መንገድ በሰላም ይተማል አጃቢ ሳያሻው ዘላለም ይኖራል የዝምታው ድምጸት ከመብረቅ ጽኑ ነው አለት ከሚያነቃ ከሚሰነጥቀው እርሱ ተረጋግቶ ሀገር ይረበሻል የለህም የሚለው እንቅልፍ አጥቶ ያድራል ከብዙ ግርግር አባይ ከዋለበት እውነት ከሚመስል አሳች ከበዛበት ዘንድሮም ጉዳዩ ከእውነት ጋር ብቻ እውነትና እውነት ከራሱ ጋር ብቻ በውሸት ከተማ እውነት እንግዳ ነው መስሎ ጸጉረ ልውጥ የሚያውቀው ሞኝ ነው እውነትን በተቀማ ትውልድ ማን ይሆን የእውነት ዘመድ ሁሉ ገሸሽ ሲል የአመጽ ቤት ሲደራ ማን አብሮ ይዘምታል ከባይተዋር ጋራ የታመነ ጓዳው ዮሴፍ ትንሹ ዛፍ ባልዋለበት ቢውል በእመቤቲቱ አፍ ከእመቤትስ በላይ ሹምስ ማንን ያምናል በሃጥእ ዘመን ዘንድ ጻድቅ ወህኒ ይወርዳል ምን ቢታፈን ሃቁ በሚያልፍ ባለጊዜ በማያልፍ ተክሷል ደርሶ የእውነት ጊዜ ባደባባይ ቢያፍር እውነትን አንግሶ ክብሩም ባደባባይ ይኸው ተመልሶ ሀብት ነው ጌጥ እውነት ምን ቢያጡም ለጊዜው ከርሞ ሚመነዘር ከፋይ ለከፈለው እውነትን በተቀማ ትውልድ ማን ይሆን የእውነት ዘመድ ብርሃን ቃሉን ሲሰጥ ጨለማን ሲደክመው የእውነት ቤት ይደምቃል ለ እግዚአብሔር ያደረው ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ እውነት እግዚአብሔር ነው የማይለውጥ ጽኑ በሰልፍ ብዛት የማይደክመው ከበረታው በላይ ብርቱ ባህሪው ሰላም ነው አያምንም በሁከት ራሱን ለማሳመን አይገባም ከጭንቀት ህሊና ወዳጁ ጊዜ መፍቻ ቁልፉ ተረጋግቶ ይኖራል ተከድቶ በስንቱ ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ ጽኑ