የትም ባክኜ እንዳልጠፋ እንደሌላቸው ተስፋ አምላኬ ጐዳናዬን መንገዴን አሰፋ ደረቁ ምድረ በዳ በውሃ እንዲረካ በምንጩ ደስ አሰኘኝ ጨለማዬ ፈካ የመርገም ጨርቄን ቀደደዉ መተላለፌን አራቀዉ እግሬን አጸና በከፍታ ወዶ አዳነኝ የኔ ጌታ በተከበበች ከተማ አጽናኝ ድምጽ እያሰማ በአስደናቂ ምሕረቱ አኖረኝ በቤቱ ሲጠብቀኝ መች ሰንፎ አቤት ስንቱን አሳልፎ ከቶ አለ ለታምራቱ ከልቤ ተጽፎ በባዕድ ምድር ጓደኛዬ (ጓደኛዬ) ሳዝን መጽናኛዬ (መጽናኛዬ) ታሪኬን ሞላው በመዝገቡ ከፍ ይበልልኝ ታላቅ ስሙ አፌን ሞላው በሳቅ ዝማሬ ተረጋጋ ዙሪያ ሰፈሬ ስለ ሥሙ ያደረገው ምስጋናው እጅግ ብዙ ነው (2x) ጌታ ፊት አይቶ አያዳላ አምላኬ የምስኪን ጥላ ተማምነው ለጠበቁት ይደርሳል ሲጠሩት እኔም እርሱን ታምኜ በእድሜ በሕይወት ዘመኔ አልቀረሁም በከንቱ አለሁኝ በቤቱ አባ አባት ብዬ ተጣርቼ (ሥሙን ጠርቼ) በእምባ በጸሎት ደጅ ጠንቼ ምልጃዬን ሰምቶ (ምልጃዬን ሰምቶ) አልጨከነም (ምሕረቱን ከእኔ) ምሕረቱን ከእኔ አላራቀም አፌን ሞላው በሳቅ ዝማሬ ተረጋጋ ዙሪያ ሰፈሬ ስለ ሥሙ ያደረገው ምስጋናው እጅግ ብዙ ነው (7x) ምስጋናው እጅግ ብዙ ነው (3x)