Song Lyrics

ኢየሱስ

Dawit Wolde
Mezmur 91
ሥምህን ሳስጠራ በዝማሬ በቤትህ ስኖር እስከዛሬ አይጠገብም ከማር ይጥማል ሥምህ ከሥሞች ሁሉ ይልቃል ያንተን ውለታ ነፍሴ ተረድታ ታከብርሃለች ጠዋትና ማታ ታከብርሃለች ቀንና ማታ ቀናት አለፉ እንደ ጥላ አምና ካቻምና ቀረ ከኋላ ባሳለፍኳቸውዘመኞቼ አፍሬ አላወቅም አንተን ጠርቼ የጸና ክንድ ነው መሸሸጊያ ጌታዬ ስምህ መጠለያ ካለም ጥፋት ማምለጫ ጥላ አዝ፦ ኢየሱስ ጌታዬ አምላኬ እኔ ከቶ አልጠግብም ሥምህን ጠርቼ ብዙ ምስጋናህን ዘምሬ መስክሬ አባ አባት ብሎ ማነው ያፈረ አንተን ተማምኖ ከስሮ የቀረ ጻድቅ ተርቦ ዘሩ ሲለምን በታሪክ የለም አልሰማንም ለኔስ ማትረፍ ነው ቤትህ መኖሬ ያንተን ምስጋና መዘመሬ ቅዱስ ሥምህን መመስከሬ አዝ፦ ኢየሱስ ጌታዬ አምላኬ እኔ ከቶ አልጠግብም ሥምህን ጠርቼ ብዙ ምስጋናህን ዘምሬ መስክሬ (2x) ኢየሱስ ሥምህ እንደሚፈስ ዘይት ነው አጥንትን ሁሉ ዘልቆ እንደሚገባ ነፍስንም እንደሚያረሰርስ ቁስልንም እንደሚፈውስ መልካም መዓዛ ያለው ዘይት ነው ለክቡር ሥምህ እዘምራለሁ ኢየሱስ (ኢየሱስ) ጌታዬ (ጌታዬ) መድህኔ (መድህኔ) አመልክሃለሁ
Mezmur debter

Ethio Christian Lyrics Collection