ግራና ቀኜን ላንተ ትጉ አድርገው ቀንሳለ ልሩጥህ መንግስትህን ላስፋው ደጆቼ ተከፍተው ብርሃኔም በርቶ የመንግስትህ ጉዳይ ያጥምደኝ በዝቶ ይብዛልኝ መታዘዜ ይብዛልኝ ላንተ መሮጤ ይብዛልኝ የመንግስትህ ጉዳይ ይክበደኝ ከሌላው በላይ ኢያኤል ያቺ ሴት ግራዋም ቀኙዎም ታዛዥ በድንኳን ከሚኖሩ ከሴቶች ይልቅ የተለየች ውሀ ለለመነ ወተት ሰጪ በከበረ ዳካ ሲሳራን የዘረረችው በእግሯ ስር አጋድማ ግራዋን ለካስማ ቀኝ እጇን ለመዶሻ በጥበብ የተሞላች ጠላትን የዘረረች የሆነች ታታሪ ለመንግስትህ ሰሪ የሆነች ሰራተኛ ለስራህ የማትተኛ ግራና ቀኜን ላንተ ታታሪ አድርገው ቀንሳለ ልሩጥህ መንግስትህን ላስፋው ደጆቼ ተከፍተው ብርሃኔም በርቶ የመንግስትህ ጉዳይ ያጥምደኝ በዝቶ ይብዛልኝ መታዘዜ ይብዛልኝ ላንተ መሮጤ ይብዛልኝ የመንግስትህ ጉዳይ ይክበደኝ ከሌላው በላይ በችግር በመከራ በፅናት ወንጌል ሰባኪ በድንጋይ ተወግሮ ማልዶ ለወንጌል ዘማች ግርፋት ደዌ ማያስቆመው በእፉኝት መነደፍ ዕለት ዕለት ሚያሳስበው የመንግስትህ መስፋት ሁልጊዜ ደስ የሚለው ታስሮ እንኳን የማይከፋው እንደ ጳውሎስ የጀገነ እስከ ሞት የቆረጠ የሆነ ሰራተኛ ለወንጌል የማይተኛ የሆነ ታታሪ ለመንግስትህ ሰሪ በዚች አጭር እድሜ መላኬን ዘንግቼ ለራሴ ጉዳይ እንዳይሆን ሩጫዬ ከእናቴ ማህፀን ጀምሮ ከለየኝ የኔ ብሎ እሮጣለሁኝ ከስጋ ከደም አልማከርም *2 ይብዛልኝ መታዘዜ ይብዛልኝ ላንተ መሮጤ ይብዛልኝ የመንግስትህ ጉዳይ ይክበደኝ ከሌላው በላይ