ሃሩሩ በረደ ጥላ በዝቶ ከጥሜም እረካሁ ውኃ ፈልቆ በቃ ሲል አበቃ መጨነቄ አሻገርከኝ ያንን ዘመን ጌታዬ አዝ፦ ያላለፍኩት ምን አለ በአንተ ጌታ ያልወጣሁት ምን አለ በአንተ ኢየሱስ ያልወረድኩት ምን አለ በአንተ ጌታ ያልተሻገርኩት ምን አለ በአንተ ኢየሱስ ተመሥገን በአንተ ሁሉን ችዬ አለፍኩት (4x) ሁልጊዜ ይነገር ስለ አንተ ነገር ስለ አንተ ዝና እስቲ ይወራ ያለፈ ይናገር ስለ አንተ ነገር ስለ አንተ ዝና እስቲ ይወራ አልተለየኸኝም በጭንቀቴ ደግፈህ አቆምከኝ መድኃኒቴ አጸናኸው እግሬን እንደ ዋላ እግር ከልቤ ልበልህ ተመሥገን አዝ፦ ያላለፍኩት ምን አለ በአንተ ጌታ ያልወጣሁት ምን አለ በአንተ ኢየሱስ ያልወረድኩት ምን አለ በአንተ ጌታ ያልተሻገርኩት ምን አለ በአንተ ኢየሱስ ተመሥገን በአንተ ሁሉን ችዬ አለፍኩት (4x) ሳስበው ወደ ኋላ ዞር ብዬ ከችግር የተነሳ ተጨንቄ ማን ያሳልፈኛል ያልኩትን አንተ እኮ ነህ ያሳለፍከኝ ጌታዬ አዝ፦ ያላለፍኩት ምን አለ በአንተ ጌታ ያልወጣሁት ምን አለ በአንተ ኢየሱስ ያልወረድኩት ምን አለ በአንተ ጌታ ያልተሻገርኩት ምን አለ በአንተ ኢየሱስ ተመሥገን በአንተ ሁሉን ችዬ አለፍኩት (4x) ሁልጊዜ ይነገር ስለ አንተ ነገር ስለ አንተ ዝና እስቲ ይወራ ያለፈ ይናገር ስለ አንተ ነገር ስለ አንተ ዝና እስቲ ይወራ (2x)