ዋላ ወደ ውሃ ምንጭ እንደምትናፍቅ ነፍሴ ወደ አንተ ትገሰግሳለች ዋላ ወደውሃ ምንጭ እንደምትናፍቅ ነፍሴ ወደ አንተ ትገሰግሳለች ቅርቤ ሆነህ ግን ነክቼ ያልጨረስኩህ የምትገባኝ ግን አውርቼ ያልቋጨሁህ የጨበጥኩህ ግን እሮጬ ያልደረስኩብህ የማወራህ ግን በቂ ቃል ያጣሁልህ እየበላሁህ የምትርበኝ እየጠጣሁህ የምትጠማኝ እየበላሁህ የምትርበኝ እየረካሁህ የምትጠማኝ ሁሌ እያየሁህ የምትናፍቀኝ ሁል ጊዜ አንተ ነህ የምታሰኘኝ አብሬህ እየዋልኩ የምትናፍቀኝ ሁል ጊዜ አንተ ነህ የምታሰኘኝ የተማርኩህ ግን እንዲህ ነህ የማልልህ ያስደነቅኸኝ ግን በቂ ቃል ያጣሁልህ የማብራራህ የቃል አቅም የሚያጥረኝ ያንተ ፍቅር እንዲህ ነው የሚያደርገኝ የልቤ አምላክ የምከተልህ እስካይህ ድረስ የምናፍቅህ የልቤ አምላክ የምከተልህ እስካይህ ድረስ የምናፍቅህ የበረሃ ጥሜን ያረካሁብህ አንተ የህይወት ውሃዬ ነህ የበረሃ ጥሜን ያረካሁብህ አንተ የህይወት ውሃዬ ነህ የምወድህ ውዴ የማፈቅርህ ፍቅሬ የምከተልህ እረኛዬ ምሰግድልህ አምላኬ አንተን ከአገኘሁ ሁሉን እረሳለሁ አንተን ከአገኘሁ ረክቼ አድራለሁ አንተን ከአገኘሁ ሁሉን እረሳለሁ አንተን ከአገኘሁ ረክቼ አድራለሁ