Song Lyrics

አልባስጥሮስ

መንገዴን አደራ ብዬ ሰጠሁት ለመድኃኒቴ ከሁሉ አስቀድሜ ከወዳጅ ዘመድ ከእናት ከአባቴ ዛሬን አየሁኝ በደግነቱ በምሕረቱ አቀዳጀልኝ ዓመታቶቸን በቸርነቱ ታማኝ ነው ታማኝ ነው እኔም በተራዬ ላክብረው ታማኝ ነው ታማኝ ነው እኔም በተራዬ ላክብረው ዘመን ከመጣልኝ እኔም በተራዬ ላክብረው ተራው ከደረሰኝ እኔም በተራዬ ላክብረው አዳኜ ኢየሱስን እኔም በተራዬ ላክብረው ክብር የሆነልኝ እኔም በተራዬ ላክብረው እግዚአብሔር ትልቅ ነው ማንንም ዓይንቅም ደካማን በመጣል እርሱ አይታወቅም ሰው የረሳውን ያስባል የተጣለውን ያነሳል ማን ወድቆ ቀረ ተጥሎ ደጅ ተጥሎ ደጅ ማን ወድቆ ቀረ ተጥሎ ደጅ ተጥሎ ደጅ መንገዴን አደራ ብዬ ሰጠሁት ለመድኃኒቴ ከሁሉ አስቀድሜ ከወዳጅ ዘመድ ከእናት ከአባቴ ዛሬን አየሁኝ በደግነቱ በምሕረቱ አቀዳጀልኝ ዓመታቶቸን በቸርነቱ ታማኝ ነው ታማኝ ነው እኔም በተራዬ ላክብረው ታማኝ ነው ታማኝ ነው እኔም በተራዬ ላክብረው ዘመን ከመጣልኝ እኔም በተራዬ ላክብረው ተራው ከደረሰኝ እኔም በተራዬ ላክብረው አዳኜ ኢየሱስን እኔም በተራዬ ላክብረው ክብር የሆነልኝ እኔም በተራዬ ላክብረው ክረምት ሆነ በጋ አይቀያየርም ቀን የጐደለለትን ጀርባውን አሰጥም አቅም ለሌለው ወገን አለኝታ ለደከመው ሰው ብርታት መከታ እውነትም አባት የሁሉ ጌታ የሁሉ ጌታ እውነትም አባት የሁሉ ጌታ የሁሉ ጌታ ትዝ ሲለኝ ውለታው ኢየሱስ ለእኔ ያረገው አይሆንልኝ ዝም ማለት ታሪኬ እኮ ነው ሰው የሆንኩበት አልባስጥሮሴን ልስበረው ውዴ ኢየሱስን ላክብረው የእኔ ክብር የእኔ ደስታ ሲከብርልኝ ነው ይህ ጌታ አልባስጥሮሴን ልስበረው ውዴ ኢየሱስን ላክብረው የእኔ ክብር የእኔ ደስታ ሲከብርልኝ ነው ይህጌታ
Mezmur debter

Ethio Christian Lyrics Collection