ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አንተ የሁሉ መድሃኒት በቸርነት እየደገፍክ ታኖረኛለህ በሕይወት ምስክር ነኝ ለሰራኸው ብዙ ተዓምር አይቼአለሁ አምላኬ ሆይ ስለ ፍቅርህ በየዕእለቱ እደነቃለሁ አዝ፦ ይገርማል የአንተ ምህረት ይገርማል የአንተ ፍቅር ይገርማል የአንተ ሥራ ያኖረኛል ከአንተ ጋራ ያኖረኛል ከአንተ ጋራ አቁሞኛል ከአንተ ጋራ አቁሞኛል ከአንተ ጋራ (2x) ቀኑን ስትጠብቀኝ ውለህ ጌታ ሌሊቱን አትተኛ በመውጣቴ በመግባቴ ሆነኸኛል ቸር እረኛ መች ያልቅና የአንተ ሥራ በየዓይነቱ ብዘረዝር ቃል አጣሁ እጄን በአፌ ጭኜ ከመደነቅ በቀር አዝ፦ ይገርማል የአንተ ምህረት ይገርማል የአንተ ፍቅር ይገርማል የአንተ ሥራ ያኖረኛል ከአንተ ጋራ ያኖረኛል ከአንተ ጋራ አቁሞኛል ከአንተ ጋራ አቁሞኛል ከአንተ ጋራ (2x)