ምሕረቱ ገንኖ በእኔ ላይ መልካም የሆነውን ቀን እንዳይ ጨለማዬን ሁሉ አብርቶአል ሃዘን ትካዜም ከእኔ ርቋል አንደበቴን ልክፈት ልናገር ያደረገልኝን ድንቅ ነገር መልካምነቱ ህሉ ይሰማ በእርሱ ዘንድ ዓይኖርም ጨለማ እርሱ የእኔ ወዳጅ እርሱ የእኔ እረኛ ( ለምን እሰጋለሁ ለምን ልቤ ይፍራ ዓለቴ ነው ጌታዬ ጽኑ ነው መሠረቴ እኔ ክፉን አልፈራም ኢየሱስ አለ በሕይወቴ ሃላፊው እርሱ ነው በእኔ ላይ ልረፍ እንጂ እኔ ምን አሰጋኝ? ብጨነቅ ባወጣው ባወርደው አንድም የለም የምጨምረው ታማኝ ነው የእኔ እረኛ የማይደክም ከቶ የማይተኛ ሃሣቤን በእርሱ ላይ እጥላለሁ ይረዳኛል አምኜዋለሁ በቸርነቱ እጄን ይዞ ትላንትናን እንዳሳለፈኝ ለዛሬውም አምላኬ አለልኝ ለምን ልፍራ ምን አስጨነቀኝ? ምሕረቱና ቸርነቱ ሁልጊዜ ይከተሉኛል አይተወኝም ለዘለዓለም ኢየሱሴ ቃል ገብቶልኛል