ንተ ሰባኪ ሆይ ስማኝ አንተ ሰባኪ ሆይ በያደባባዩ መዳንን ላጣ ሰው ለማይሞላ ሆዱ ተስፋን ስታጎርሰው አለምን መረጠ ከኢየሱስ ስራ በወንጌል መጫሚያ ንዋይ ስትጠራ አንተ ሰባኪ ሆይ ስማኝ አንተ ሰባኪ ሆይ አንድም ስንወድቅ ነው አንድም ስንነሳ የኢየሱስ ስራ በኛ የሚወሳ ትሾማለህ ብቻ ትበላለህ ብቻ ማዳኑን አትተካ በገንዘብ እንጎቻ [አዝ] የጠበቀህ እንዲሁ 'ካስፈሪ ማዕበል ከልሎኝ ነቅ እንጂ ሀይሌ ነው አትበል በእኔነት ካባ አለባብሰው ቢያርሱ (ኃላ ለአረም ነው) የሚገልም እሱ የሚያድንም እሱ [አዝ] አእላፋት በ'ጆችህ ባ'ደራ ሲሰጡ አንተን ሊከተሉ ከየጫፍ ቢመጡ ባውርቷ'ደር መሃል ባ'ስመሳይ ጎዳና በኑሮህም አፅና የቃልህን ዳና [አዝ]