የክብር ልብሷን ለብሳ እንደ ቆመች ንጉሱ ፊት የወርቁንም ዘንግ እንደ ነካች ጥያቄዋን እንደመለሰላት እኔም ኢየሱስን ለብሼ አብ ፊት ሞገስ አገኘው አባባት ማለት ድፍረቴ ተመለሰልኝ ወደ ህይወቴ አባቴ የማለት እምነቴ ተመለሰልኝ ወደ ቤቴ የመማጸኛ ከተማዬ ዘልዬ የማመልጥበት ከአሳዳጅ ከአስጨናቂዎቼ ተሸሽጌ ምገባበት ኢየሱስ በተባለው ድንቅ ስም ነፍሴ አርፋለች ከምንም እርሱ የከፈለውን ዋጋ አልፎ ማነው እኔን ሚነካ በደም የከፈለውን ዋጋ ደፍሮ ማነው እኔን ሚጠጋ ከሳሾቼ ብዙ ናቸው ተጨባጭ መረጃ አላቸው በህጉ መሰረት ቢሄዱ አሳማኝ ነው ምክኒያታቸው በየትኛው ቅድስናዬ ልጋፈጥ ልቁም ለራሴ አንገት መድፋት መሸማቀቅ ዝምታ ብቻ እንጂ መልሴ የቤቴ ክፍተት ሳይገፋው ገፍቶ ባይገባ ከደጄ የልቤ ርቀት ሳይመልሰው ባያቅፈኝ ባይሆን ወዳጄ ሁሉን በራሱ ፈጽሞ ባያደርገኝ ኖሮ ቀና ጽድቄ ብዬ ማስቆጥረው የማሳየው ምን አለና ፍርድ አልተዛባም ልክ እኮ ነው ተከድኖ ሳይሆን ተከፍሎ ነው በከንቱ አይደለም ደስታዬ ኢየሱስ ሆኖኝ ነው ይቅርታዬ ፍርድ አልተዛባም ልክ እኮ ነው ተከድኖ ሳይሆን ተከፍሎ ነው በከንቱ አይደለም ደስታዬ ስለሆነኝ ነው ይቅርታዬ ያሸነፈልሽ ተሸነፈ ጌታሽ አበቃለት ሲሉኝ የሞተውን እንኳ ስጡኝ ያልኩበት ምክኒያት አለኝ የኔ እነደሌላው መች ሆኖ ቀርቦኝ ሲያጫውተኝ ቤዛዬ አሳ ማጥመድ ወይ በሰው ፊት ሚወራ አልነበረም ስራዬ በሀጢያተኞች ገበታ እንዴት ይቀርባል ሲሉት እኔን ከመውደዱ አልቦዘነም ከክብሩ በልጬበት ታዲያኮ አማራጭ የሌለው ሙሉ ልቡን የሰጠ ሰው ክብሩን ከመጣል ከመሸነፍ ከመውደድ ማን ሊመልሰው ፍርድ አልተዛባም ልክ እኮ ነው ተከድኖ ሳይሆን ተከፍሎ ነው በከንቱ አይደለም ደስታዬ ኢየሱስ ሆኖኝ ነው ይቅርታዬ ፍርድ አልተዛባም ልክ እኮ ነው ተከድኖ ሳይሆን ተከፍሎ ነው በከንቱ አይደለም ደስታዬ ስለሆነኝ ነው ይቅርታዬ ይቅርታዬ ይቅርታዬ