ትልቁ እግዚአብሔር ለኔ ለትንሿ አባት ነው ዘመድ ኩራት መጏደጃ ልክ እንደ አንድ ልጅ እንደ ብቸኛ የምትሳሳልኝ የነፍሴ እረኛ ትርፍ አይደለሁም ለቤትህ ወይ በጎደለ ልሞላ ብጠፋ ፈላጊዬ እትተካኝም በሌላ ዘጠና ዘጠኝ እያሉህ ሞልቶ እያለ በመንጋ አይኖችህ ክርትት እያሉ እኔን አንዲቷን ፍለጋ ባጠፋም ልጅህ ነኝ ባለማ በመልካም በክፉ ብታማ ውድ ነው የእኔ ልጅነት በደል ያልፋል አባትነትህ ነፍሴን መለስካት ስለ ስምህ በፅድቅ መራኸኝ ስለ ስምህ ቀንና ለሊት ስለ ስምህ ተከታተልከኝ ስለ ስምህ ልክ እንደ አንድ ልጅ እንደ ብቸኛ የምትሳሳልኝ የነፍሴ እረኛ አባ አባቴ እያልኩኝ ወደ ዙፋንህ ስጠጋ ከብዙ ጥፋት በኋላም አልተለወጠም ፀጋህ ቀድሞስ መቼ ተወደድኩኝ በጨዋነቴ በእኔ ስራ አንተው ዘንድ አይደለም ወይ የፍቅርህ መነሻ ስፍራ ባጠፋም ልጅህ ነኝ ባለማ በመልካም በክፉ ብታማ ውድ ነው የእኔ ልጅነት በደል ያልፋል አባትነትህ ላንተ የዋለ ሳይታጣ እኔን ቁምነገር እድርገህ መጣ ባልበቃም እንኳን ባልመችህ እየታገስከኝ አለሁ ቤትህ ልክ እንደ አንድ ልጅ እንደ ብቸኛ የምትሳሳልኝ የነፍሴ እረኛ በመኖሬ ደስ የሚልህ በመጥፋቴ የሚያምህ አባቴ ነህ ከአባትም አባት እድሜ ዘመኔን የምኮራበት