ብዙ ፍጥረት ያለው ባህር ውቅያኖሱ ለየብስ እሩብ ሰጥቶ ቀሪውን መልበሱ ላጥፋ ካለ አጥፊ ጡንቻ ያለው ፈርጣማ ከአንዱ ጌታ በቀር ማንንም አይሰማ ጥም አርኪ ይመስላል ግን ለጠማው ደሃ ውስጡ ስለሌለ ለመጠጥ የሚሆን አንድ ብርጭቆ ውሃ ሰነፍ መርከበኛ ውቅያኖሱ ዳር ሚጠጣውን ሳይዝ መጓዝ ቢጀመር ውሃ መሀል ደርሶ ውሃ ይጠማዋል ውሃ በረሐ ላይ በውሃ ጥም ይሞታል አንድ ጉድጓድ አለች በጣም ትንሽዬ ሕፃን ነህ አዋቂ ጨዋ ነህ ዱርዬ ሳትል ሳታዳላ ሁሉን ታጠጣለች ይሄን ንፁህ ውሃን ታመነጨዋለች ጠቢቡ ገበሬ እሷ ዳር ይዘራል ስሩ ምንጯን ነክቶ ማን ደርቆ ይቀራል ጌታ ኢየሱስን በእምነቱ የነካ ከሕይወት ውሃ ምንጭ ጠጥቶ ረካ ስንት ምስኪን አለ ሳይተኛ ሚያነጋ ነፍሱ ምትገረፍ በጥማት አለንጋ እግዚአብሔር ነፍሱን ነይ ላርካሽ ቢላት የእግዚአብሔርን ሳይሆን ለነፍሱ ሆዱን ሰማላት ጌታ በሌለበት በዛ ባዶ ቦታ ምኑንም ቢከቱ አይሰጥም እርካታ ሰማይና ምድር በአንዴ ተጠቅልሎ የኢየሱስን ቦታ አይሞላውም ችሎ የተከበበ በማይጠጣ በአለም ያለ ሰው ኢየሱስን ያጣ በጀልባው እንደጠፋ ውቅያኖስ ላይ ኢየሱስ የሌለው ሰው እሱ አይደል ወይ? ተበልቶ ተጠጥቶ የለም እርካታ ኑሮ ማለት ሐሩር ከሌለው ጌታ ዳግም አልጠማኝም አንዴ ጠጥቼው ጎዶሎ የለኝም ውስጤ ሙሉ ነው (2x)