በእርግጥ አይሏል ማእበሉ ቅጥሏል ብሶ ትግሉ አማራጭ ተስፋ ሲጠፋ ጊዜውም ሄደ እየከፋ መጠጊያ ከለላ ቢፈለግ ሁሉም ሚገባበት ቢያጣ ከማዶ በባህሩ ላይ እየተረማመደ መጣ አይዟቹ አትፍሩ እኔ ነኝ ያለው የባህሩ ጌታ ጸጥ አድርጎ ሁሉንም ማእበሉን ከመንገዴ ገታ ትናንት ዛረ ዘላለም ያው ነው አይለወጥ ጌታ አለ በዙፋኑ ላይ የኔንም ችግር ሊፈታ *2 አለ አለ የኔ አባት አለ ትናንትና እንደነበረ ዛረም ደሞ በዚ አለ ለነገም ተስፋየ እሱ ነው ዝም ብዬ አመልከዋለው ተስፋ ሲጨልም ቀኑ ሲመሽ የተደገፉትም ሲሸሽ ብቸኝነቱም ሲበረታ መኖርም ትርጉም ያጣ ለታ ሸክም ከብዶ ሲያንገላታ ድካሙ እጅግ ቢበረታ ወደ እኔ ያለው ኢየሱስ እረፍት የሚሰጥ ያለአፍታ እኔ ካንተጋ ነኝና አትፍራ ብሎኛል ጌታ ሸክሜን ያራገፈው ቀንበሬን ከላዬ እየመታ ተስፋዬን አድሶ ያቆመኝ እሱ ነው የነፍሴ ቤዛ ታሪኬን የቀየረው እንድኖር በሱ ታዛ ህይወቴን የቀየረው እንድኖር በሱ ታዛ አለ አለ የኔ አባት አለ ትናንትና እንደነበረ ዛረም ደሞ በዚ አለ ለነገም ተስፋየ እሱ ነው ዝም ብዬ አመልከዋለው አለ በዙፋኑ ላይ የተጨነቀ የሚያይ አለ ማደሪያው አርጎኛል ውዱ መንፈስ ቅዱስ አለ በዙፋኑ ላይ የተጨነቀን ሚያይ አለ በክብር ግርማው ላይ በአብቀኝ በሰማይ አለ ደሞ በእኔ ውስጥ የነገስታቱ ንጉስ አለ ማደሪያው አርጎኛል ውዱ መንፈስ ቅዱስ አለ አለ የኔ አባት አለ ትናንትና እንደነበረ ዛረም ደሞ በዚ አለ ለነገም ተስፋየ እሱ ነው ዝም ብዬ አመልከዋለው