እኔን መታገል አልችልም በራሴ ሞክሬ ወደቅኩኝ አድክሟታል ነፍሴ ነገር ግን አለና ከእኔ የበረታ እርሱን ስሻው አለሁ እልሀለሁ ጌታ እኔን መታገል አልችልም በራሴ Chorus ከእኔ በላይ ጸጋህ የበረታ ይያዘኝ ሳይለቀኝ አይልቀቀኝ ለአፍታ ከእኔ በላይ ጸጋህ የበረታ ይያዘኝ ሳይለቀኝ አይልቀቀኝ Verse 2 የተከበብኩበት እሾኹ ነው ብርቱ የዚህ ዓለም ኃሳብ የማያልቅ ምኞቱ ላቆጥቁጥ ስል ደርሶ ፈጥኖ እንዳያንቀኝ ቀድመህ ድረስና ልቤን ለም አድርግልኝ Chorus ከእኔ በላይ ጸጋህ የበረታ ይያዘኝ ሳይለቀኝ አይልቀቀኝ ለአፍታ ከእኔ በላይ ጸጋህ የበረታ ይያዘኝ ሳይለቀኝ አይልቀቀኝ Verse 3 እለምንሀለሁ እንድትሰማኝ አባ ጸጋህ ካላገዘኝ ጨለመብኝ በቃ ስጋና ስሜቴ እንዳይመራ ሕይወቴን ቶሎ እርታኝ እና ባርክልኝ ዘመኔን እኔን መታገል አልችልም በራሴ Chorus ከእኔ በላይ ጸጋህ የበረታ ይያዘኝ ሳይለቀኝ አይልቀቀኝ ለአፍታ ከእኔ በላይ ጸጋህ የበረታ ይያዘኝ ሳይለቀኝ አይልቀቀኝ