በጣር በበዛ ስቃይ በነፍስ ድካምህ አባትህ ጨከነ ፊቱን አዞረብህ ለወጉህ እየማለድክ ውርደት ላለበሱህ ቁጣውን አበረድክ እጅጉን ለጠሉህ ቸር የሆንህ በምህረትህ ባለጠጋ አንድም የለም ካንተ ፍቅር የሚጠጋ የቆሰልህ የተበሳህ ልታርቅ ነው ከእኔ አበሳ ፈውሴ ነህና 2x ብቸኛ መዳኛ 2x ኢየሱስ ብቸኛ 2x ከሕይወት ልታደርሰኝ ደምህ ጎረፈ መስዋእትነትህ ውድቀቴን አለፈ ፀጋህ ፈሰሰልኝ ተደግፌው ቆምኩኝ ላትሰርዝ ላትተወኝ አንዴ ወደድከኝ 3x አንዴ መረጥከኝ3x ማነው ሚለየኝ3x አንዴ ወደድከኝ3x የማልወጣበት ከመሰለኝ እንዳልንቀሳቀስ ጠፍሮ ከያዘኝ እራሴን ካወረድኩበት ከከተትኩበትም አዘቅት ክንድህ ይደርሳል ከሲኦል አይርቀውም እኔን ለማስጣል እልፎቹን በጎች እየተወ አንዷን እኔን ሲል ከነፈ ቸር የሆንህ በምህረትህ ባለጠጋ አንድም የለም ካንተ ፍቅር የሚጠጋ የቆሰልህ የተበሳህ ልታርቅ ነው ከእኔ አበሳ ፈውሴ ነህና 2x ብቸኛ መዳኛ 2x ኢየሱስ ብቸኛ 2x የማይነጥፍ ጅረት ነው ፍቅርህማ ውዴ ቃልህን ፈፀምከው እንዳትጥለኝ አንዴ በድካም በዝለት እጅግ እየበረታ በአብ ፊት መታያ ይኸው ሆኖልኛል እኔን ልታነግሰኝ ዋጋ የከፈልከው በጌቴሴማኔ ነፍሴን ባንተ ያረከው በሕይወት ኑሪ ያልከኝ ማቄን ቀደህክኝ አንዴ ወደህ መረጥከኝ ይህ ነው መልሕቅ የሆነኝ አንዴ ወደድከኝ 3x አንዴ መረጥከኝ3x ማነው ሚለየኝ3x አንዴ ወደድከኝ3x