እንዴት ያለውን ፍቅርህን ነው ያደልከን የማይነጥፈው ሰላምህን ያካፈልከን እንዴት ያለውን ምህረት ነው ያገነንከው ለጠፋሁትኝ መስዋዕት ሆነህ የቀረብከው እንዴት ያለውን ክብር ነው ያለበስከን በፀጋህ ብዛት ድህነትን ያጎናፀፍከን እንዴት ያለውን ውስጣዊ ሰላም ደስታ አበዛህልኝ ጋረድከኝ ከአለም ሁካታ የአባትህን ፍቃድ ልትፈፅም ነው ፍፁም ታዘህ አቀረብከኝ ዳግም ወደ ራስህ ቤዛ ሆነህ አንተ የኔ አባት እኔም ያንተ ልጅ ሆኛለው ማንም ላይለየን ኪዳናችን በቅዱስ ደምህ ነው ፅድቅ አልብሰኸኝ ኩነኔን ከኔ አርቀኸዋል የሚከስኝ የለም አንዴ ወደህ መርጠኸኛል ታማልዳለህ ልታኖረኝ በፅድቅ ህይወት ዘመኔን ከብረህ ዘላለሜን በውበት ልትታይበት ለኔ ለኔ ነው ይህንን ሁሉ የሆንከው ለኔ ብለህ ነው ደምግባትህን ውበት ያጣኸው አዎ ለኔ ነው ክብርህን ትተህ የተዋረድከው በሚጠሉህ ፊት ጎልጎታ ላይ የታየኸው ኢየሱስን በማወቅ ወደሚገኝ በረከት ይኸው ገባሁኝ ፅድቅ ሆነህልኝ በእምነት ስለክብሩ ልኖር ተሾምኩኝ እንደመልካም ልጅ በክብር ስም ተጠራሁ ተያዝኩኝ በአንተ እጅ ለምን ወደድከኝ ስለራሴ ይገርመኛል ከኔ አንዳች የለም አውቃለሁ ይህ ገብቶኛል እንደምትወደኝ ለሞት ታዝዘህ አሳይተሃል አቤት እላለው ከአይምሮዬ በላይ ሆነህብኛል ለኔ ለኔ ነው ይህንን ሁሉ የሆንከው ለኔ ብለህ ነው ደምግባትህን ውበት ያጣኸው አዎ ለኔ ነው ክብርህን ትተህ የተዋረድከው በሚጠሉህ ፊት ጎልጎታ ላይ የታየኸው