Song Lyrics

በሕይወት መዝገብ ጻፍከኝ

Diyakon Hawaz tegegne
Special Edition
በህይወት መዝገብ ፃፍከኝ በጽድቅህ ጻድቅ ሆንኩኝ ሰርቼ ሳይሆን በስራ ዳንኩኝ በፀጋ በሀጢያት የሞትኩኝ በህግ የተገደልኩ ሳለው ገና በአመፃ እያለው ጠላትህ እየሆንኩ ሳለው ገና ባንተ በልጁ ሞት ታረቀኝ አባትህ ቸር ጌታዬ በችንካርህ ብዕር ፃፍከኝ በመዝገብህ ቸር ጌታዬ የማያሳፍር ተስፋ ማይደበዝዝ የፅድቅ ብርሃን የማያሳዝን ተስፋ ማይቆጠር ልዩ ዘመን በዓይን ያልታየ ርዕስት ሀገር አለኝ በአባቴ ዘንድ መጥተ ትወስደኛለህ ጌታ ኢየሰስ የኔ መንገድ ጻፍከኝ በሕይወት መዝገብ ጻፍከኝ የኔ ስራ ሳይሆን ተቆጥሮልኝ ስራህ ድኛለው መዝኖ ከሀጢያቴ የሚጮሀው ደምህ ድኛለው ከህይወት መዝገብ ላይ መልአኩ አያጣኝም ድኛለው በፅድቅህ ተፅፌ ኩነኔ አይፍቀኝም ድኛለው አልጠፋም ከመዝገብህ በመንፈስህ ታትሜአለው ሊደመሰስ እንዳይችል ጌታ ባንተ አምኛለው በዚያ የህይወት መፅሀፍ ስሜ አለ በሰማያት በደምህ ወርሻለው ገብቻለው ወደ እረፍት ጻፍከኝ በሕይወት መዝገብ ጻፍከኝ ነውር የሌለበት እንድሆን በፊቱ የመረጠኝ የንጉስ ካህን አድርጎ የለየኝ ለዕርስቱ የመረጠኝ የእርሱን በጎነት ለዓለም እንድናገር የመረጠኝ ወደ ብርሃን ጠራኝ ከጨለማው መንደር አከበረኝ ከድቅድቁ ጨለማ ወደ ሚደንቅ ልዩ ብርሃን ጠራኸኝ ሙሽራዬ ወደ ክብርህ ልዩ ዙፋን በፀጋህ ነው የዳንኩት ከቶ አይደለም በኔ ስራ ዋስትናዬ ደምህ ነው እንዳልሰጋ እንዳልፈራ ለሀጢያት ፈቃድ አይደለም መዳኔና ነፃነቴ የእንደልብ ኑሮ እንዳይሆን የደም ዋጋ አለው ሕይወቴ ስጋዬ ደክሞ ብስት እንዳይገድለኝ ሀጢያት ደግሞ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለኝ የሚታይልኝ ለኔ ቀድሞ
Mezmur debter

Ethio Christian Lyrics Collection