ምህረትህ በዛ ጌታዬ ምህረትህ በዛ ምህረትህ በዛ ኢየሱስ ምህረትህ በዛ በዙሪያዬ ያለው ሲነጥፍ ደመና ከሰማይ ሲገፈፍ ልብ የተጣለበት ሲሰበር ተስፋ አካል ሳይለብስም ሲቀር አሁንስ ተስፋዬ ኸረ ማን ነው ሮጬ ማመልጠውስ ወዴት ነው /2* አንተ ግን በቃ አልክ ቃልህን ለኔ ላክ ተስፋዬን አደስከው ብርሃን ይሁን ብለህ ጨለማውን ገፈፍከው ፊትህን ልፈልግ ማልጄ ድምፅህን ለመስማት ጓጉቼ በእጆችህ መዳሰስ ናፍቄ መገኘትህን ሽቼ ከልቤ ማነክስባቸው ድካሞቼ ፊቴ ሲደቀኑ ፈ ር ቼ ልነሣ ስዳዳ ከፀሎቴ ምህረትህ እንደ ወንዝ ገባ ቤቴ አጠብከኝ በደምህ ተሰማኝ ያ ድምፅህ ፊትህም በራልኝ አንተ'ኮ ልጄ ነህ በርታ ጽና አልከኝ