ናና እየው ወዴት እንዳኖርኩት በልቤ ጓዳ ሸሽጌ ያኖርኩትን እኔና አንተ ብቻ በምናውቀው ጉዳይ መልስ እጠብቃለሁ ከሰማይ ኢየሱስ ላንተ ብቻ ባወጋሁ ጉዳይ መልስ እጠብቃለሁ ከሰማይ እየጠበቅሁ ነው ከትናንት ዛሬ አዳምጣለሁኝ ኮቴህን ከበሬ እጠብቅሃለሁ በመጠበቂያዬ አላሳንስህም በአንደበቴ ዝዬ ኮሽ ባለ ቁጥር አልደናበርም እየጠረጠርኩህ እምነቴን አልጥልም አንተ ላይ ነው አቅሜ የጩኸቴ ብርታት አቤቱ አቤቱ አቤት የምልበት ናና እየው ወዴት እንዳኖርኩት በልቤ ጓዳ ሸሽጌ ያኖርኩትን እኔና አንተ ብቻ በምናውቀው ጉዳይ መልስ እጠብቃለሁ ከሰማይ ኢየሱስ ላንተ ብቻ ባወጋሁ ጉዳይ መልስ እጠብቃለሁ ከሰማይ ደጅህን ብጠና እንደው ብመላለስ ፊትህን አትቀጭምም ከበር እንድመለስ ኮቴዬን ስትሰማ አይዝህም ዝለት የልቤን ተማጥኖ ቸል የምትልበት በተስፋ ለሚሹህ ለሚጠባበቁህ ታጠግባቸዋለህ ከመልካምነትህ ቢጠብቅ እስሩ ቢሸት መቃብሩ ባንተ ጊዜ ሲሆን ይሰማሀል ሁሉ አንተ ምታስበው ደግ ደጉን ብቻ መልካሙን ስለእኔ ብትነሳኝ ደሞ ብትከለክለኝ ብለህ ለጥቅሜ ብቻ ዝም አትበል አንድ ነገር በለኝ ትሁነነኝ ፍቃድህ ያልከው ይከተለኝ አይድጠኝም አፌን ለከንቱ ልሰለፍ ፀጋህ ይበቃኛል ባንተ ምክር ልረፍ