በፍቅርህ መልህቅ እኔ ተጣብቄ መልካምነትህን ጠንቅቄ አውቄ ምንም አያጓጓኝ አልሆነብኝ ራቤ ኢየሱስ አንተው ነህ የእውቀትና የጥበብ መዝገቤ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የተሰወረ ለእኔ ግን የተገለጠው በእኔ ውስጥ መሆንህ ነው ይሄ ነው የበራልኝ >> ደሰ የምያሰኘኝ >> የተገለጠልኝ >> ያስደነ'ከኝ ለተሻለ ኪዳን ለርስቱ የተለየ ወገን በፈሰሰው ደምህ ሆኛለው የንጉሥ ካህን በዘመኑ ፍጻሜ ያለ ሥጋት በነፃነት እንድኖር አብ ካሰየኝ ፍቅር አይኖረኝም የሚበልጥ ክብር ተማርኪያለው ባንተ እኔ ተሸንፌያለው ከማይጠፈው ዘር በመንፈስ ተወልጃለው ካንተ ውጭ የለም በልቤ የሾምኩት ንጉሥ በሕይወቴ ተሞገስ የነፍሴ ጌታ ኢየሱስ ካንተ ጋር የዋሉ ከእጅህም በልተው የለመዱ እውነቱን ስትገልጠው ጠፉ ሁሉም እያጎረመረሙ ከሚጠፋው ዓለም ርቆ ለተከተለህ ፊትህን ለሚሻው ጴጥሮስም በእምነት አንተን ነው የሕይወት ቃል ኣለህ ያለው እኔም አሃ ለማያልፈው ለዘላለም ኑሮዬ ብዬሃለው አንተን ብቻ የሕይወት እንጀራዬ የማትርቅ የማትጠፋ ሁሌ ከአጠገቤ እውነት ሕይወት መንገዴ ገበተኻል በልቤ አብን የተረክልኝ መንፈስህን የሰጠኸኝ ምንም እስከ ማይገርመኝ ድረስ ያስደነከኝ አንተው ነህ ጌታዬ ለራስህ የለየኸኝ